CARD FactCheck

CARD FactCheck

Share

Fact-checking election information using iVerify. Promoting verified and trusted public information. Join our Telegram channel: https://t.me/cardfactcheck

21/07/2026

In an era of endless scrolling, how do you know what’s real? We are working around the clock to track, verify, and debunk false claims so you can make informed decisions with confidence.
Before you share, pause and ask: Is it true?
የሀሰት መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮች የወደፊት እጣ ፈንታችንን እንዲወስኑ አንፈቅድም!
ሳይንሸራሸሩ እና ሳያጋሩ በፊት ቆም ብለው ይጠይቁ፤ መረጃው እውነት ነው?
👉 Follow CARD FactCheck on Facebook and Telegram, or visit cardeth.org to stay updated with verified facts.

20/07/2026

፥ ‹‹Gumuz Voice›› የተባለ የፌስቡክ ገጽ - የሶማሌ ክልል ተወካዮች የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ካዘጋጀው ጉባኤ ለቀው መውጣታቸውን የሚገልጽ መረጃ ማጋራቱን ተመልክቷል።

የተሰራጨውን መረጃ ለማጣራት አጣሪ ቡድኑ ለኮሚሽኑን ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፥ በምላሹም እስከ አሁን ጉባኤውን የተሰናበተና ለቆ ለመውጣትም ጥያቄ ያቀረበ አካል ያለመኖሩን ለቡድኑ አሳውቋል፡፡

በዚህ መሰረት ‹‹የሱማሌ ክልል ተወካዮች የምክክር ኮሚሽኑ ህዝባችን አይጠቀምም አይወክልም የግለሰብ ሀሳብ ነው በማለት ምክክሩ ለቆ ወጥተዋል›› ተብሎ በፌስቡክ የተሰራጨው መረጃ ሐሰት መሆኑን አረጋግጧል።

The CARD Fact Checking Team found that a page called "Gumuz Voice" shared a claim that representatives from the Somali Regional State had left the conference organized by the Ethiopian National Dialogue Commission, saying the commission does not benefit or represent their people and reflects only an individual's opinion. To verify the claim, the team contacted the Commission. The Commission told the team that, as of the time of the inquiry, no participant had left the conference or requested to withdraw. Based on this response, the team confirmed that the claim shared on Facebook is false. _አጣሪ ቡድን፥ ‹‹Gumuz Voice›› የተባለ የፌስቡክ ገጽ - የሶማሌ ክልል ተወካዮች የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ካዘጋጀው ጉባኤ ለቀው መውጣታቸውን የሚገልጽ መረጃ ማጋራቱን ተመልክቷል።

የተሰራጨውን መረጃ ለማጣራት አጣሪ ቡድኑ ለኮሚሽኑን ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፥ በምላሹም እስከ አሁን ጉባኤውን የተሰናበተና ለቆ ለመውጣትም ጥያቄ ያቀረበ አካል ያለመኖሩን ለቡድኑ አሳውቋል፡፡

በዚህ መሰረት ‹‹የሱማሌ ክልል ተወካዮች የምክክር ኮሚሽኑ ህዝባችን አይጠቀምም አይወክልም የግለሰብ ሀሳብ ነው በማለት ምክክሩ ለቆ ወጥተዋል›› ተብሎ በፌስቡክ የተሰራጨው መረጃ ሐሰት መሆኑን አረጋግጧል።

The CARD Fact Checking Team found that a page called "Gumuz Voice" shared a claim that representatives from the Somali Regional State had left the conference organized by the Ethiopian National Dialogue Commission, saying the commission does not benefit or represent their people and reflects only an individual's opinion. To verify the claim, the team contacted the Commission. The Commission told the team that, as of the time of the inquiry, no participant had left the conference or requested to withdraw. Based on this response, the team confirmed that the claim shared on Facebook is false.

03/07/2026

‹‹ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና›› የተባለው የፌስቡክ ገጽ ሁለት የፒዲኤፍ (PDF) ምስሎች በማያያዝ ‹‹በዘይሴ ቀበሌዎች በንጹሃን ላይ እየተፈጸመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአስቸኳይ እንዲቆም ኢሰመጉ ጥሪ አቀረበ›› በሚል ርዕስ ስር አንድ ጽሁፍ ማጋራቱን ተመልክቷል።

መረጃ አጣሪ ቡድኑ የተሰራጨውን ይዘት ለማጣራት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ኃላፊዎችን በመጠየቅ ዘይሴ ወረዳን በተመለከተ መግለጫ ማውጣታቸውን ገልጸዋል፤ ይህንን ተከትሎ ቡድኑ ‹‹ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና›› ሰኔ 25፣ 2018 ዓ.ም ያጋራው ፒዲኤፍ ኢሰመጉ በተመሳሳይ ቀን በይፋ ካወጣው መግለጫ ጋር ተመሳሳይ መሆኑን ተገንዝቧል።

በዚህ መሠረት መረጃ አጣሪ ቡድኑ ‹‹ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና›› ፌስቡክ ገጽ ላይ የተጋራው ፒዲኤፍ እውነት መሆኑን አረጋግጧል።


The CARD Fact-Checking Team reviewed the PDF shared by the page "ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና" and contacted EHRCO officials to verify it. The officials confirmed that EHRCO had issued the statement, and the team found that the PDF shared by the page was the same as the official statement published by EHRCO. Therefore, the team confirmed that the PDF is authentic.

23/06/2026

፥ ‹‹ወሎ አዲስ›› በተባለ የፌስቡክ ገጽ ላይ “ባለ ቁልፉ ወሎ ፓርቲ አንድም የምርጫ ክልል ሳያሸነፍ ቀረ” በሚል ያሰራጨውን ይዘት ተመልክቷል።

አጣሪ ቡድኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ ውጤቶችን እና ከፓርቲው አስተባባሪ የወሎ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ባገኘው መረጃ መሰረት፥ ፓርቲው በአማራ ክልል፣ በአዲስ አበባ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በእያንዳንዳቸው አንድ አንድ በጥቅሉ አራት የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎችን አሸንፏል።

ይህንንም ተከትሎ አጣሪ ቡድኑ ‹‹ወሎ አዲስ›› ሰኔ 15፣ 2018 ዓ.ም በማኅበራዊ ሚዲያ ያሰራጨው ‹‹የወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲ ፓርቲ አንድም የምርጫ ክልል ሳያሸነፍ ቀረ›› የሚለው መረጃ ሐሰት መሆኑን አረጋግጧል።

The CARD Fact-Checking Team checked a claim shared by the page “ወሎ አዲስ” saying that the Wollo People's Democratic Party did not win any election constituency. After checking the official election results from NEBE and information from the party coordinator, the team found that the party won four regional council seats, one each in Amhara Region, Addis Ababa, Southwest Ethiopia, and Central Ethiopia. Therefore, the claim that the Wollo People's Democratic Party did not win any constituency is false.

19/06/2026

በዛሬው ዕለት ካጣራቸው ይዘቶች መካከል “ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና” የተባለ የፌስቡክ ገጽ ያጋራውን ደብዳቤ ይመለከታል።

ገጹ ከደብዳቤው በተጨማሪ በሰበር ዜና “በዘይሴ ልዩ ምርጫ ክልል በምርጫ አስፈጻሚዎችና ዕጩዎች ላይ በብልጽግና ፓርቲ የቀረበው ክስ ውድቅ ተደረገ !!” የሚል ሰፊ ሐተታ አጋርቷል።

መረጃ አጣሪ ቡድን ደብዳቤውንና የደብዳቤውን ይዘት በተመለከተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባገኘው መረጃ መሰረት፥ በ‹‹ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና›› የተሰራጨው ደብዳቤና የደብዳቤው ይዘት እውነት መሆኑን አረጋግጧል።


A page called “ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና” which has more than 10K followers, shared a post with an attached letter claiming in a breaking news update that: “The complaint filed by the Prosperity Party against election officials and candidates in the Zeyse Special Electoral Constituency has been dismissed”

The CARD Fact-Checking Team verified the letter and its contents using information obtained from the National Election Board of Ethiopia. The team confirmed that the letter circulated by “ዘህዴድ ዕለታዊ ዜና›” is authentic and that its contents are accurate. Therefore, the claim is true.

17/06/2026

ከ60 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ‹‹ Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ›› የተባለ የፌስቡክ ገጽ ባጋረው መረጃ ‹‹እሸቱ ኃይሌ ደስታ በሶዶ ምርጫ ክልል ከወሎ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ተወካይ በመሆን ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ተመርጠዋል” የሚል ልጥፍ አጋርቷል።

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ የፓርቲው አመራሮች እንደተረዳው ፓርቲው በሶዶ ምርጫ ክልል አቶ እሸቱ ማሸነፋቸውን የሚገልጽ መግለጫ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያለማድረጉን ጠቅሰው፥ ውጤቱን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ አሳውቀዋል።

ይህንን ተከትሎ አጣሪ ቡድኑ ዘቢዳር ሚዲያ ያጋራው መረጃ አሳሳች መሆኑን አረጋግጧል።

17/06/2026

ከ140ሺህ በላይ ተከታይ ያለው ‹‹DMN – Dubusha Media Network›› የተባለ የፌስቡክ ገጽ ባሰራጨው ቪዲዮ፣ የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በምርጫ ውጤት ላይ ያቀረበውን ቅሬታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውድቅ ማድረጉን ይገልጻል።

ከምርጫ ቦርድ ባገኘው መረጃ መሰረት ቦርዱ የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ያቀረበውን ቅሬታ ከመረመረ በኋላ ውድቅ ማድረጉን አረጋግጧል። ቦርዱ ቅሬታው የምርጫ ውጤቱን ለመቀየር ወይም ለመሰረዝ በቂ የሕግና የእውነታ መሠረት እንዳልነበረው ገልጿል። ይህም ውሳኔ ለፓርቲው በይፋዊ ደብዳቤ መገለጹን አስታውቋል።

መረጃ አጣሪ ቡድኑ ከምርጫ ቦርድ ባገኘው መረጃ መሠረት፤ ቦርዱ የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ቅሬታን ውድቅ ማድረጉ እውነት መሆኑን አረጋግጧል።

16/06/2026

ከ25ሺህ በላይ ተከታይ ያለው ‹‹የዳርባ ሚዲያ›› የተባለ የፌስቡክ ገጽ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ‹‹በአማሮ ምርጫ ክልል የሕዝቡ ውሳኔ ትክክል ነው›› በማለት የብልጽግና ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ ያቀረበውን ቅሬታ ውድቅ ማድረጋቸውን የሚገልጽ መረጃ ይዞ ወጥቷል።

ይህንን ጥያቄ ለማረጋገጥ ፥ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችን ጠይቆ እንደተረዳው ከቀረበው የቅሬታ ደብዳቤ ጋር በተያያዘ ርዕሰ መስተዳድሩ ምላሽ ያለመስጠታቸውንና በተጠቀሰው ገጽ ላይ የተያያዘው ፎቶ ከሌላ ስብሰባ ላይ የተወሰደ ስለመሆኑ ምላሽ ሰጥተዋል።

መረጃ አጣሪ ቡድኑ ከርዕሰ መስተዳድሩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ከሌሎች ምንጮች ባገኘው መረጃ መሠረት በፌስቡክ ገጹ ላይ የተሰራጨው ይዘት ሐሰት መሆኑን አረጋግጧል።

15/06/2026

በቲክቶክ ሥሙ ‹‹Gibe Insight›› የተባለ ገጽ ‹‹የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከነገ ጀምሮ በየክልሉ ምርጫ ከመረጠን ህዝባችን ጋር ውይይት ይጀመራል ›› ከሚል ጽሁፍ ጋር አንድ ተንቀሳቃሽ ምስል በማያያዝ በሰበር ዜና መረጃውን አጋርቷል፡፡

፥ ይዘቱን እንዳጣራው ከሆነ ‹‹Gibe Insight›› የተባለው ገጽ የተጠቀመው ቪዲዮ መጋቢት 6 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ያስተላለፉትን ንግግር ከያዘ የዩትዩብ ገጽ ላይ ተቀንጭቦ የተወሰደ መሆኑን አረጋግጧል፡፡

ከሁለት መቶ ሺህ በላይ ዕይታዎችን ያገኘው ይህ መረጃ የሰባተኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ አስታኮ ከአራት ዓመታት በፊት የተሰራጨን ቪዲዮ በዚህ ሳምንት ውስጥ እንደተላለፈ በማስመሰል ከአውድ ውጪ ተጠቅሟል፡፡

በመሆኑም የካርድ መረጃ አጣሪ ቡድን በተጠቀሰው የቲክቶክ አካውንት ላይ የተሰራጨው ይዘት አሳሳች መሆኑን አረጋግጧል፡፡

15/06/2026

በዚህ ሳምንት የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ለካርድ መረጃ አጣሪ ቡድን እንዲጣራላቸው ከላኳቸው መረጃዎች መካከል ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲን ይመለከታል፡፡ Tsegaw Tadele የተባለ የፌስቡክ አካውንት ‹‹ምርጫው ይደገም!!!›› በሚል ርዕስ ጎጎት በተወዳደረባቸው በጉራጌ እና ምሥራቅ ጉራጌ ዞኖች ምርጫው በድጋሚ እንዲካሄድ መጠየቁን የሚገልጽ መረጃ አጋርቷል።

እንደታዘበው ማኅበራዊ ገጾች ላይ ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው መረጃዎች እየተሰራጩ እንደሚገኙ ተመልክቷል።

አጣሪ ቡድኑ ይህንን ተከትሎ ይዘቱን እንዳጣራው ቦርዱ ከሰጠው መግለጫ አንጻር፥ በ120 የምርጫ ክልሎች ላይ ቅሬታ እንቀረበ ተረድቷል። ከነዚህ ቅሬታ አቅራቢዎች መካከል ጎጎት ፓርቲ አንዱ ሲሆን፥ በተጨማሪም ቅሬታ ባቀረቡባቸው የምርጫ ክልሎች ላይ ምርጫ እንዲደገም ከጠየቁ ፓርቲዎች መካከል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) እና ሌሎች ፓርቲዎች እንደሚገኙ አጣርቷል።

መረጃ አጣሪ ቡድኑ ከቦርዱና ከፓርቲዎቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ፓርቲዎቹ ቅሬታ ማቅረባቸው እውነት መሆኑን አረጋግጧል።

Want your organization to be the top-listed Non Profit Organization in Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address

Addis Ababa
Ababa